Welcome to Salale University’s (SlU) Official Website,It is my great honor to serve as the President of Salale University, and I am deeply inspired to work alongside the dedicated and enthusiastic staff of our institution. I firmly believe that education is the most powerful tool to drive national progress and improve lives in all dimensions. It serves as the foundation for all forms of advancement, achievable only when access and equity are ensured.
With this vision, and guided by our motto, "Co-Creating Quality," Salale University was established in 2015 in Fiche town, North Showa Zone, Oromia Region, located 112 kilometers from Addis Ababa. Since its inception, SlU has been steadfastly committed to its three core missions: education, research, and community service. The University began its academic journey with nine undergraduate programs. Today, it offers more than thirty undergraduate programs, and we have finalized preparations to launch postgraduate programs in various fields by 2020. Our region, North Showa, widely known as "Salale" for historical reasons, is uniquely positioned, bordered by two major tributaries of the Nile River—Mogor and Jama—as well as the Nile itself. This area has attracted significant attention from researchers and academics due to its potential mineral resources.
Read More...| Su | M | Tu | W | Th | F | Sa |
|---|
በሰላሌ ኦሮሞ ባህል ማዕከል የተሰጠውን የሶስት ቀን ስልጠና ያዘገጀው የሰላሌ ዩኒቨርሲቲ የሴቶች ህጻናት፤ወጣቶች ጉዳይ ዳይሬክቶሬት ሲሆን በስልጠናው የተሳተፉት ደግሞ ከተለያዩ የአስተዳደር ከፍሎች የተውጣጡ ከ100 በላይ የሚሆኑ ሴት
የአስተዳደር ሰራተኞችና አካል ጉዳተኞች ናቸው፡፡ ስልጠናውም የተሰጠው ከኢትዮጲያ ስራ አመራር ኢንስቲትዩት በመጡ አሰልጣኞች ነው፡፡
በስልጠናው ፕሮግራም ላይ በመገኘት የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የሰላሌ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ገናነው ጎፌ እንደተናገሩት የአገልግሎት አሰጣጣችንን ከግዜ ወደ ጊዜ በማሻሻልና በማዘመን ቀልጣፋና ዘመናዊ በማድረግ እነዲሁም የዩኒቨርሲቲውን ግብ ለማሳካት ስልጠናው ጉልህ አስተዋጽዖ አለው በማለት ስልጠናውን እስከ መጨረሻው በትጋትና በንቃት እዲከታተሉ ለሰልጣኞቹ መልእክት አስተላልፈዋል፡፡
ስልጠናው በዋናነት ያተኮረው በደንበኞች አገልግሎት አሰጣጥ ስነ ምግባር ዙሪያ፣ የመልካም አስተዳደር መሰረታዊ መርሆች ፣ከአገልጋይ ሰራተኛ ምን ይጠበቃልና ወዘተ የመሳሰሉትን ዋና ዋና ርዕሶች ላይ ነበር፡፡ ለሶስቱም ቀናት በነረው የስልጠና መረሃ ግብር ሰልጣኞቹ በሁለት ምድብ ተከፍለው የሰለጠኑ ሲሆን ሰፊ ውይይትና ምክክር አካሂደዋል፡፡ በውይይቱ ወቅት በሁለቱም የስልጠና ታዳሚዎች ዘንድ የተነሱትን ሃሳብ አሰተያየትና ጥያቄዎች በአሰልጣኞቹ አማካኝነት ቀርቦ በሰላሌ ዩኒቨርሲቲ ሴቶች ህጻናት ወጣቶች ጉዳይ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር በሆኑት በመምህርት ሃና ታምራት ማጠቃለያ ተሰጥቶበታል፡፡
በሰላሌ ዩኒቨርሲቲ የአስተዳደርና ተማሪዎች ጉዳይ ም/ፕሬዝዳንት አቶ አዱኛ መኮንን በስልጠናው መዝግያ ፕሮግራም ላይ በመገኘት ባደረጉት ንግግር በስልጠናው ያገኘነውን እውቀተና ከህሎት ይበልጥ በማጎልበት የአገልግሎት አሰጣጣችንን በማዘመን ሁላችንም ባለንበት የስራ ክፍል የበኩላችንን ሃላፊነት ከተወጣን ዩኒቨርሲቲውን ወደ ላቀ ደረጃ ማድረስ እንችላለን በማለት ም/ፕሬዝዳንቱ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡ በመቀጠልም ም/ፕሬዝደንቱ፤ የዩነቨርሲቲው ሴት አስተዳደር ሰራተኞች ስልጠናውን በላቀ ምግባር በመከታተል እንዲሁም ገንቢ ሃሳብ፤ አስተያየትና ጥያቄዎቻቸውን በሰለጠነ መንገድ በማቅረብ ላሳዩት መልካም አርኣያነት ያላቸውን አድናቆትና ምስጋና ችረዋል፡፡
በመጨረሻም አንዳንድ የስልጠናው ተሳታፊዎች እንደተናገሩት በተሰጣቸው ስልጠና የተደሰቱ መሆኑን ገልጸው፤ ስለ ለደንበኞች አገልግሎት አሰጣጥ መሰረታዊ መርሆችና ለአገልግሎቱ ብቁ የሚያደርጉ ነገሮች ላይ ያላቸውን የግንዘቤ ክፍተቶች ያሟላላቸው በመሆኑና በስልጠናው ያገኙትን እውቀትና ክህሎቶች ወደ ተግባር በመቀየር የዩኒቨርሲቲውን ማህበረሰብ እንዴት ማገልገል እንደሚቻል ብዙ ግንዛቤ ማገኘታቸውን ተናግረዋል፡፡