Welcome to Salale University’s (SlU) Official Website,It is my great honor to serve as the President of Salale University, and I am deeply inspired to work alongside the dedicated and enthusiastic staff of our institution. I firmly believe that education is the most powerful tool to drive national progress and improve lives in all dimensions. It serves as the foundation for all forms of advancement, achievable only when access and equity are ensured.
With this vision, and guided by our motto, "Co-Creating Quality," Salale University was established in 2015 in Fiche town, North Showa Zone, Oromia Region, located 112 kilometers from Addis Ababa. Since its inception, SlU has been steadfastly committed to its three core missions: education, research, and community service. The University began its academic journey with nine undergraduate programs. Today, it offers more than thirty undergraduate programs, and we have finalized preparations to launch postgraduate programs in various fields by 2020. Our region, North Showa, widely known as "Salale" for historical reasons, is uniquely positioned, bordered by two major tributaries of the Nile River—Mogor and Jama—as well as the Nile itself. This area has attracted significant attention from researchers and academics due to its potential mineral resources.
Read More...| Su | M | Tu | W | Th | F | Sa |
|---|
በጄኔራል ታደሰ ብሩ ዋና ግቢ የስድስት ቀን የስልጠና መርሃ ግብር ያዘጋጀው የሰላሌ ዩኒቨርሲቲ የኢንተርፕሪነርሽፕ አና ቢዝነስ ኢንኩቤሽን ሴንተር ዳይሬክቶሬት ሲሆን
በስልጠናው የተሳተፉት ደግሞ ከተለያዩ ኮሌጆችና ትምህርት ክፍሎች የተወጣጡ ከ60 በላይ የሚሆኑ የዩኒቨርሲቲው መምህራን ናቸው፡፡ ስልጠናውም የተሰጠው ከኢትዮጲያ ሥራ ፈጠራ አመራር ኢንስቲትዩት በመጡ አሰልጣኞች ነው፡፡
ስልጠናው በዋናነት ያተኮረው በስራ ፈጠራ መሰረታዊ የንግድ ንድፈ ሃሳብ ማፍለቅ፤ የስኬት መንገዶች፤በዓለም አቀፍ ደረጃ ያሉት በስራ ዘርፍ የስኬት መልካም ተሞክሮዎች፤ ከስልጠና በኋላ ከሰልጣኞች ምን ይጠበቃልና ወዘተ በመሳሰሉት ዋና ዋና ርዕሰ ጉዳዮች ነው፡፡ ሰልጣኞቹም በሁለት ምድብ ተከፍለው የሰለጠኑ ሲሆን ስልጠናውም ተግባር ተኮር ስራዎች ላይ ያተኮረና ተግባራዊ የአመለካከትና የባህሪ ለውጥ የሚያመጣ ስልጠና ነው፡፡
በስልጠናው መዝጊያ ፕሮግራም ላይ በመገኘት የመዝጊያ ንግግር ያደረጉት የሰላሌ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ገናነው ጎፌ እንደተናገሩት እንዲህ አይነቱ ስልጠና በሁሉም በተሰማራንበት የስራ ዘርፍ በቡድንም ሆነ በግል በምንኖረው ህይወት ውስጥ ስኬታማ ስራ እንድንሰራና የእያንዳንዳችንን የኑሮ ደረጃ ድሮ ከነበርንበት ወደ ፊት የሚያራምድና ከግልም አልፎ ለአገር እድገት እጅግ የጎላ አስተዋጽኦ ያለው ስለሆነ ከስልጠናው የተገኘውን እውቀትና ክህሎት እንዲሁም በአገርና በዓለም አቀፍ ያሉትን መልካም ተሞክሮዎች ወደ ተግባር በመቀየር ብሎም ለሌሎች ማህበረሰብ አርአያና ምሳሌ በመሆን የበኩላችንን ድርሻ ከተወጣን የምንፈልገውን ሁሉ በቅርብ ግዜ ማሳካት ይቻላል ብለዋል፡፡
በስተመጨረሻም አንዳንድ የስልጠናው ተሳታፊዎች እንደተናገሩት በተሰጣቸው ስልጠና የተደሰቱ መሆኑን ገልጸው፤ስለ ስራ ፈጠራ ብቁ የሚያደርጉ መሰረታዊ የስራ ፈጠራ ክህሎቶችን ወደ ተግባር በመቀየር ስኬታማ ስራ እንደሚሰሩ አስተያየት ሰጥተዋል፡፡ በስልጠናው የሚጠበቅባቸውን አስፈላጊ ሁኔታዎችን በብቃትና በንቃት ላጠናቀቁ ሰልጣኞች የተሳትፎ ምስክር ወረቀት ተሰጥቷል፡፡